በካማሺ ዞን የዳምቤ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት

  • Home
  • Greece
  • Agálo
  • በካማሺ ዞን የዳምቤ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት

በካማሺ ዞን የዳምቤ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት በካማሺ ዞን የዳምቤ ወረዳ የመንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት

ለሀገር ስላም፤ ለሀገር ልማት ዳምቤ ከተማ ክረምት በጋራ በሚል መሪ ሀሳብ የከተማ ጽዳት ተካሄደ ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም ዳምቤ — የዳምቤ ወረዳ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ከመንግሥት...
08/09/2026

ለሀገር ስላም፤ ለሀገር ልማት ዳምቤ ከተማ ክረምት በጋራ በሚል መሪ ሀሳብ የከተማ ጽዳት ተካሄደ

ጳጉሜ 3/2018 ዓ.ም ዳምቤ — የዳምቤ ወረዳ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ከመንግሥት ጎን ለጎን በመቆም በወረዳው በበጎ አድራጎት ስራ ላይ በመሳተፍ በከተማው ውስጥ ለውስጥ በመዛወር የጽዳት ስራ አካሂደዋል።

ፖስተር ደገፈ ከሰሰ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ለዳምቤ ወረዳ ማህበረሰብ በአስተላለፈው መልዕክት የበጎ አድራጎት ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደአለበት ገለፃው እርስ በእርስ መተባበር መተጋገዝ ልጅ እናት አባቱን መክበር ተገቢ መሆኑ አስገንዝበዋል።

ፖስተር ደገፈ አክለውም በዕለቱ በተካሄደው የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት ምዕመናን በጸሎትና በዝማሬ በመሳተፍ መንፈሳዊ በረከትን ተቀብለዋል። በመርሃ ግብሩም ለምዕመናን እምነታቸውን እንዲያጠናክሩ፣ በፍቅርና በአንድነት እንዲኖሩ የሚያበረታታ መልዕክት አስተላልፈው ከመንግስት በልማት ስራ መተባበር እንደአለበት ጠቅመዋል።

በአደባባይ በተደረገው የወንጌል ስብከት መርሃ ግብር ወረዳው በጸሎት አስቧል። በመርሃ ግብሩ ላይ የወንጌል ቃል ለተሰበሰቡ ምዕመናንና ሕዝቡ ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነት እንዲጠብቁ አስተምህሮ ተሰጥቷል።

የተደረገው የወንጌል ስብከት ማኅበረሰቡ በእምነትና በመልካም ሥራ እንዲጸና፣ በሰላምና በመቻቻል እንዲኖር የሚያበረታታ መልዕክት አስተላልፏል።

በዚህ መሠረት ለአቅመ ደካማ፣ አካል ጉዳተኛ ፣ ወላጅ አልባ ህጻናት ለበዓል የልብስና የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ የበጎ አድራጎት ስራ ሰርተዋል።

በመርሀ ግብሩ የተሳተፉ የከተማ መዘጋጃ ቤት ሀላፊ ገረሙ በየነ የወረዳው ሴቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ሀልካነ ስልካ የተደረገው የበጎ አድራጎት ስራ የሚበረታታ መሆኑ ገልጸው ሌሎች የሀይማኖት ተቋምም አብዛኛው ሰው የሚገኝበት ስለሆነ ከመንግስት ጎን ለጎን በመቆም በሰላም ፣ በልማት እንዲሁም በበጎው አድራጎት ስራ መሳተፍ መልካም ስራ መሆኑ አስገንዝበዋል።

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ70 ሺህ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋበትምህርት ዘመኑ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች...
22/08/2026

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ70 ሺህ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

በትምህርት ዘመኑ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች መካከል 70 ሺህ 544 የሚሆኑት ማለፋቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የፈተናውን ውጤት አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ በማምጣት ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚቀላቀሉት ተማሪዎች 12.8 በመቶ ሲሆኑ፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር አበረታች ለውጥ የታየበት መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ባለፈው ዓመት ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ያሳለፉ ትምህርት ቤቶች ቁጥር 62 የነበረ ሲሆን፣ በዘንድሮው ዓመት ይህ ቁጥር ወደ 88 ከፍ ማለቱን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በተቃራኒው ደግሞ ምንም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ባለፈው ዓመት ከነበረው 1 ሺህ 230 ዘንድሮ ወደ 565 ዝቅ ማለቱ በትምህርት ዘርፉ የታየው መሻሻል ማሳያ መሆኑ ተጠቁሟል።

#ኢቢሲ

የቴክኖሎጂን ቀመር ወደ መፍትሔ የመቀየር ጉዞ**************ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ከሩቅ የሚታይና ከሌሎች ሀገራት ተቀብሎ በመጠቀም ብቻ የሚወሰን የነበረበት አስተሳሰብ በፍጥነት እየተቀየ...
21/08/2026

የቴክኖሎጂን ቀመር ወደ መፍትሔ የመቀየር ጉዞ
**************

ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ከሩቅ የሚታይና ከሌሎች ሀገራት ተቀብሎ በመጠቀም ብቻ የሚወሰን የነበረበት አስተሳሰብ በፍጥነት እየተቀየረ መጥቶ፣ የወጣቶች እውቀትና ፈጠራ በኮድና በመረጃ አማካኝነት የህብረተሰቡን ችግሮች የሚፈታበት አዲስ ምዕራፍ ተጀምሯል።

ኮድ ማለት በኮምፒውተር ስክሪን ላይ የተሰለፉ ፊደላት ብቻ አለመሆናቸውን በመረዳት፣ ችግርን የሚለይና የሰዎችን ጊዜ፣ ጉልበትና ወጪ የሚቀንስ መፍትሔ አድርጎ የመጠቀም ሀገራዊ እሳቤ እያደገ መጥቷል።

ይህ ለውጥ በትራንስፖርት ዘርፍ በትራንስፖርት ጥሪ አፕሊኬሽኖች፣ በፋይናንስ ዘርፍ በሞባይል ባንኪንግና በዲጂታል ክፍያዎች፣ በግብርና ዘርፍ ለገበያ መረጃ ማድረሻ መድረኮች እንዲሁም በጤናው ዘርፍ ታካሚዎችን ከህክምና ባለሙያዎች ጋር በሚያገናኙ የስታርትአፕ ስኬቶች በግልጽ እየታየ ይገኛል።

ኢትዮጵያ ከ2030 የዲጂታል ኢትዮጵያ ዕቅድ ጋር የሚራመድ የሰው ኃይል ለመገንባት ከወሰደቻቸው ታላላቅ እርምጃዎች መካከል የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች የስልጠና ኢንሼቲቭ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው።

ይህ ኦንላይን ስልጠና ወጣቶች የራሳቸውን ሀሳብ ወደ ዲጂታል ምርት እንዲቀይሩ የሚያስችላቸውን ቁልፍ ክህሎቶች የሚያስጨብጥ ነው።

5 ሚሊዮን የሰለጠኑ ዜጎችን ማፍራት ችግርን በፈጠራ የሚመለከቱ አእምሮዎችን፣ ግዙፍ የመፍትሔ አቅምን እና አዳዲስ የስታርትአፕ እድሎችን መፍጠር በመሆኑ፣ ወጣቶች ይህንን ሰፊ የስልጠና ዕድል በመጠቀም ሀገርን ወደተሻለ የዲጂታል ከፍታ የሚያሸጋግር የታሪክ አካል እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።

በልዩ እሸቱ


EBC

የተጀመሩ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ ገለፁ።የክረምት ወራት የበጎ ፈ...
21/08/2026

የተጀመሩ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ ገለፁ።

የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራና ተረጂነትን ለማስቀረት እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች አፈፃፀም ተገምግሟል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ እንዳሉት በክረምት ወራት ለመከናወን የታቀዱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

አሁንም በሁሉም የትኩረት መስኮች የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተጠባቂ ሥራ እንዲሰሩም አስገንዝበዋል ።

በሌላ በኩል በሀገር ደረጃ ከተረጂነት ለማላቀቅ የሚያስችል ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል ።

በክልሉም በምግብ ራስን ለመቻል የሚያስችል አስቻይ ሁኔታ መኖሩን በመረዳት ያሉ ዕድሎችን ተጠቅሞ በቅንጅት መስራት እንደሚገባም አሳስበዋል ።

የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ድንቅነሽ ማሞ እንዳሉት ደግሞ በክረምት ወራት በ14 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መስኮች በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የአቅመ ደካማ ቤቶች ግንባታ ጋር ተያይዞ በበርካታ ተቋማት እስካሁን ሥራ አለመጀመራቸውን ገልፀዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና የአቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዑስማን አህመድ ክልሉ ከተረጂነት ለማለቀቅ እየተሰራ ያለውን ሥራ አስመልክተው ባቀረቡት ሪፖርት ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም የመሸፈን ውጥንን ማሳካት የሉዓላዊነት፣ የክብርና የነፃነት ጉዳይ ተደርጎ እየተሰራ ነው ብለዋል ።

ይህንን እውን ለማድረግ ያሉንን ሀብቶችን በሚገባ በመጠቀም እየሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል ።

በክረምት ወራት እየተከናወኑ ባሉ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራዎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ ይገኛሉ ያሉት የመድረኩ ተሳታፊዎች ከተረጂነት ለማለቀቅ ያሉ አቅሞችን ለይቶ መስራት የተገባ መሆኑን ገልፀዋል ።

ሪፖርተራችን ስዩም እምቢያለ እንደዘገበው !!!

ዳምቤ ወረዳ የ2019 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ግምገማ አካሄደዳምቤ፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም — ዳምቤ ወረዳ የ2019 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ግምገማ አካሂዷል።በግምገማው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዋ...
20/08/2026

ዳምቤ ወረዳ የ2019 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ግምገማ አካሄደ

ዳምቤ፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም — ዳምቤ ወረዳ የ2019 ዓ.ም መሪ ዕቅድ ግምገማ አካሂዷል።

በግምገማው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዋና ዱጉማ የ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት መሪ ዕቅድን አቅርበዋል።

በቀጣዩ የበጀት ዓመት የጤና አገልግሎትን ዲጂታላይዝ ማድረግና የገጠር ኮሪደር ልማትን በወረዳው ተግባራዊ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ አቶ ዋና ገልጸዋል።

በትምህርት ዘርፍ ያሉ የግብዓት ችግሮችን በመፍታት ከትምህርት ውጭ የሆኑ ሕፃናትን ወደ ትምህርት ማስገባት እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በግብርና ዘርፍ አርሶ አደሩ ገበያ ተኮር በሆነ ምርት ላይ እንዲያተኩር በማድረግ የምርታማነት ዕድገትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸዋል። ይህንንም ለማሳካት የአፈር ማዳበሪያን በአግባቡ መጠቀም፣ የመስኖ እርሻን ማስፋፋትና የሜካናይዜሽን አገልግሎትን ማጠናከር የግብርና ሥራን ለማዘመን ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አስገንዝበዋል።

በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ የተራቆቱ መሬቶችን በችግኝ መሸፈን ቀጣይነት ባለው መልኩ መከናወን እንዳለበትና ማህበረሰቡ የተከላቸው ችግኞች እንዲጸድቁ የቅርብ ክትትልና እንክብካቤ መደረግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የወረዳውን የፋይናንስ አሠራር ለማዘመን ዘመናዊ የፋይናንስ አሠራሮችን በመዘርጋት ለሂደቱ ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባም ተገልጿል።

በሚደራጁ የህብረት ሥራ ማህበራት የዕጣ ሼር አመዳደብና አሠራር በግልጽ ሁኔታ እንዲፈጸም ትኩረት መስጠት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም የወረዳውን የኔትወርክ፣ የመንገድና የትራንስፖርት ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት ተገቢው ሥራ እንደሚከናወን ተገልጿል።

የወረዳውን ኢኮኖሚ በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የሕግ የበላይነትን ማስከበርና ከአጎራባች ክልሎች ጋር መልካም ግንኙነትን ማጠናከር በቀጣይ የሚሠራባቸው ቁልፍ ጉዳዮች መሆናቸውም ተጠቁሟል።

የዳምቤ ወረዳ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ማሞ ገማቹ ከማዕድን ሀብት ጋር ተያይዞ ያለውን አቅም በአግባቡ በመጠቀም ማህበረሰቡና ወረዳው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተገቢው ሥራ መሠራት እንዳለበት ገልጸዋል።

የዳምቤ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የ2019 በጀት ዓመት የአርሶ አዳር ግማሜ ገቢ የግብር ድልደላ ለመድረግ ከጽህፈት ቤቱ ስራ ሂደቶች ጋር ውይይት አካሄደዋል ።‎‎የጽህፈት ቤቱ የግብር አወሳ...
20/08/2026

የዳምቤ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት የ2019 በጀት ዓመት የአርሶ አዳር ግማሜ ገቢ የግብር ድልደላ ለመድረግ ከጽህፈት ቤቱ ስራ ሂደቶች ጋር ውይይት አካሄደዋል ።

‎የጽህፈት ቤቱ የግብር አወሳሰን ቡድን መሪ አቶ ጣሊያን ትርሾ እንደ ገለጹት የግብር ድልደላው የሚሰማሩ ባለሙያዎች መደበኛ የግብር ከፋይ አርሶአደሮች ና አድስ ግብር ከፋይ አርሶአደሮች በቅድሚያ በመለየት ደንብና መመሪያ የተከተለ ሁሉም የቀበሌ መዋቅሮችን ያሳተፈ ድልደላ መድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል ።

‎የወረዳው ቀበሌዎች መብዛቱ የተነሳ ስራ በ ሦስት (3)ክላስተር ማዕከል ተከፋፍሎ እንደሚሰራ ገልጾ ሰራውን ለማፋጠን ከአሁን በቅርበት ያለቸው ክላስተር ማዕከል እንደሚጀምሩ የገቢ ግብር አሰባሰብ አወሳሰን ክትትል ስራ ሂደት ና አሰተባባሪ አቶ ቦካ ሺሬ ገልጸዋል ።

‎ለ2019 የወረዳ የውስጥ ገቢ 81.381.964 ብር ከዚህ ውስጥ የአርሶአደር 4.000.000 ብር መሆኑ የጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌታቸው ጂራታ ገልጸዋል ።

‎2019 በጀት ዓመት የገቢ ግብር አሰባሰብ አድስ የተሻሻለ የፈደራል በወጣ የግብ አወጀ መሰረት ያደረገ ስለመሆኑ ለዚህም ሁሉም ግብር ከፋይ አርሶአደሮች ከአሁን ግንዛቤ ኑሮአቸው ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለመዳረግ እንደሆነ ሃላፊው አቶ ጌታቸው ጂራታ ተነግሯል ።

‎በተጨማሪም የሚሰማሩ ሙያተኞች ድልደላ ከመደረጉ በፊት ለማህበረሰቡ በቂ ግንዛቤ መስጠት እና ፍህታዊ እንድሆን በግንዛቤው ና ድልደላው ሁሉም የቀበሌ መዋቅሮች መግኘት እንዳለባቸው አክለዋል ።

19/08/2026
ፖሊስ አባላት የወረዳውን የልማት ድርሻ በመወጣት፣ ከጸጥታ ሥራቸው ጎን ለጎን በልማትና በበጎ ፈቃድ ሥራዎች በንቃት እየተሳተፉ ነው*********(ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም ዳምቤ) የዳምቤ ወረ...
18/08/2026

ፖሊስ አባላት የወረዳውን የልማት ድርሻ በመወጣት፣ ከጸጥታ ሥራቸው ጎን ለጎን በልማትና በበጎ ፈቃድ ሥራዎች በንቃት እየተሳተፉ ነው
*********
(ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም ዳምቤ)

የዳምቤ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ኮማንደር ዳዊት ሞገስ እንደገለጹት፣ የፖሊስ አባላቱ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ከማስጠበቅ ባሻገር በወረዳው የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችንም በተግባር እየደገፉ ነው።

በተለይም በዘንድሮው የክረምት ሥራ መርሐ ግብር የፖሊስ አባላቱ የጸጥታ ሥራቸውን በማከናወን ላይ ሆነው በርካታ የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

የተረጂነትን ቁጥር ለመቀነስና የማህበረሰቡን የምግብ ራስን መቻል ለማሳደግ እየተከናወነ ባለው የእርሻ ልማት ሥራም የፖሊስ አባላቱ የወረዳውን ድርሻ በመወጣት በንቃት ተሳትፈዋል።

እንደ ኮማንደር ዳዊት ገለጻ፣ ይህ ተሳትፎ የጸጥታ ተቋማት ሚና ከሕግና ሥርዓት ማስከበር ብቻ የተገደበ ሳይሆን ለሀገርና ለማህበረሰብ የሚጠቅሙ የልማት ሥራዎችን በመደገፍ የጋራ ኃላፊነትን ማሳየት እንደሚገባ ያሳያል።

የዳምቤ ወረዳ ፖሊስ አባላትም በቀጣይ ከመንግሥትና ከሕብረተሰቡ ጎን በመቆም የልማት፣ የሰላምና የሕዝብ አገልግሎት ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለማጠናከር ዝግጁ መሆናቸውን ኮማንደር ዳዊት ሞገስ ገልጸዋል።

ከተረጂነት ቅነሳ የሚደረገው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል የዳምቤ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቡራቃ ተደሰ   *********ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም፣ ዳምቤበዳምቤ ወረዳ ከተረጂነት ቅነሳ ጋር ተ...
18/08/2026

ከተረጂነት ቅነሳ የሚደረገው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል የዳምቤ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቡራቃ ተደሰ
*********
ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም፣ ዳምቤ

በዳምቤ ወረዳ ከተረጂነት ቅነሳ ጋር ተያይዞ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን በማጠናከር የክረምት እርሻ ልማት ሥራዎች በሁሉም የሴክተር መሥሪያ ቤቶች ተሳትፎ እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ።

የዳምቤ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቡራቃ ተደሰ ወረዳው ከተረጂነት ቅነሳ እና ከአምራችነት ማሳደግ ጋር ተያይዞ በሚያከናውናቸው ሥራዎች ሁሉም የሴክተር መሥሪያ ቤቶች ሠራተኞች በቁርጠኝነት እየተሳተፉ ነው።

የወረዳው ተፈጥሮ ሀብት ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ክብሩ ጀለታ በበኩላቸው፣ ከተረጂነት ቅነሳ ጋር ተያይዞ በወረዳው በየቀበሌው የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አቶ ክብሩ ገለጻ፣ መሥሪያ ቤቱ በ8 ሄክታር መሬት በቆሎና ቦሎቄ በማልማት በያዘው የዓመቱ ዕቅድ መሠረት ሥራውን እያከናወነ ይገኛል። የተዘራው ሰብል ውጤታማ እንዲሆንና የተሻለ ምርት እንዲሰጥ የእርሻ እንክብካቤና የአረም ቁጥጥር ሥራዎችም በወቅቱ እየተከናወኑ ነው።

የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ ተገኝ ፋይሳ በበኩላቸው፣ መንግሥት በያዘው የአምራችነት ማሳደግና ከተረጂነት ቅነሳ አቅጣጫ ወረዳው እየወሰደ ያለው እርምጃ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል። ሁሉም የመንግሥት ሠራተኞችም ለልማት ሥራው ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር እያሳዩ መሆኑን ጠቁመዋል።

የዳምቤ ወረዳ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ አቶ ገራሙ በያነ ባለፈው ዓመት ከተረጂነት ቅነሳ ጋር ተያይዞ በተሠራው ሥራ የወረዳው ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ሆኗል። በተለይም የከተማው ማኅበረሰብ ከተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ በዘንድሮው ዓመትም ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አክለዋል።

የዳምቤ ወረዳ አመራርና የሴክተር መሥሪያ ቤቶች ሠራተኞች በጋራ የሚያከናውኑት ይህ የልማት ሥራ ከተረጂነት ቅነሳ በተጨማሪ የምግብ ዋስትናንና የማኅበረሰቡን አምራችነት ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑ ተጠቁሟል።

ዳምቤ ወረዳ ወላጅ ለሌላቸው ሕፃናት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ****ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም ዳምቤየዳምቤ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቡራቃ ተደሰ ወረዳው በያዝነው ዓመት ወላጅ ለሌላቸ...
13/08/2026

ዳምቤ ወረዳ ወላጅ ለሌላቸው ሕፃናት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
****
ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም ዳምቤ

የዳምቤ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቡራቃ ተደሰ ወረዳው በያዝነው ዓመት ወላጅ ለሌላቸው ሕፃናትና ለአቅመ ደካሞች የአልባሳት፣ የምግብ ፍጆታ፣ የገንዘብ እና ሌሎች ድጋፎችን መደረጉን ይታወሳል ብለዋል።

በተጨማሪም የወረዳው ሴክተር መሥሪያ ቤት በበጎ ፈቃድ ሥራ በመሳተፍ ማህበረሰቡን በመደገፍ የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑን አቶ ቡራቃ ጠቁመዋል።

በዚህ መሠረት ቀጣይ ለማህበረሰቡ፣ በተለይም ድጋፍ የሚሹ አካላት የሚያደርገውን ትብብር እንደሚያጠናክር ምክትል አስተዳዳሪው ተነግሯል።

Address

Agálo

Telephone

+251980248884

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በካማሺ ዞን የዳምቤ ወረዳ መንግስት ኮሙንኬሽን ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share