Ethiopian Embassy in Riyadh / የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ሪያድ

Ethiopian Embassy in Riyadh / የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ሪያድ This is the official Facebook handle of the Ethiopian Embassy in Riyadh, Saudi Arabia
(5)

This is the official page of the Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia in the Kingdom of Saudi Arabia.

በኦማን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ተመሠረተ=====(ሪያድ፣ ጳጉሜ 1 ቀን 208 ዓ.ም) በኦማን ሱልጣኔት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን መብት፣ ክብርና ጥቅም ለማስጠበቅ እንዲሁም ህብረታቸውን ለማጠ...
06/09/2026

በኦማን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ተመሠረተ
=====
(ሪያድ፣ ጳጉሜ 1 ቀን 208 ዓ.ም) በኦማን ሱልጣኔት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን መብት፣ ክብርና ጥቅም ለማስጠበቅ እንዲሁም ህብረታቸውን ለማጠናከር የሚያስችል የኮሚኒቲ ማህበር በሙስካት ተመሠረተ።


በምስረታው ላይ የተገኙት በሳዑዲ አረቢያና በኦማን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር፣ መንግሥት ለዜጋ-ተኮር ዲፕሎማሲ የሰጠውን ትኩረት መሠረት በማድረግ ከማህበረሰቡ አባላት ጋር በአገልግሎት አሰጣጥና በዜጎች መብት ማስጠበቅ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።


አምባሳደሩ በውይይቱ ወቅት ማህበሩ ከኢትዮጵያ ኤምባሲና ከኦማን የሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት፣ የመብት ጥሰቶችን ለመከላከልና ጠንካራ ድልድይ ለመሆን ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል። አክለውም ዜጎች ከህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር አደጋ ተጠንቅቀው በህጋዊ መንገድ ብቻ እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ አቅርበዋል። አምባሳደሩ የዜጎችን ህጋዊ የሥራ ዕድልና መብት ለማስከበር የቤት ሠራተኞችን፣ የሰለጠኑና ከፊል የሰለጠኑ ሙያተኞችን የሚያካትት የሥራ ስምሪት ስምምነት መንግስታችን ከኦማን መንግሥት ጋር ለመፈራረም የመጨረሻ መግባባት ላይ መድረሱንም አብስረዋል።


በታሪካዊው የምስረታ መድረክ ላይ የተሳተፉት የኦማን ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ማህበረሰቡን የሚያገለግሉ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን በነጻነት መርጠዋል።

በምስረታው በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሚሲዮኑ ምክትል መሪ አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ እንዲሁም የቆንስላና የዳያስፖራ ጉዳዮች ኃላፊዎች ተገኝተው ኤምባሲው ለኮሚኒቲው አስፈላጊውን ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም፣ በኦማን ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በቅርብ አገልግሎት የሚሰጥ ሚሲዮን በቅርብ ጊዜ ለመክፈት የሚያስችል አስፈላጊው ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑ አምባሳደሩ አብስረዋል።

06/09/2026

በረያድ እና አከባቢዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን የ2018 ዓም ጳጉሜ 5 ለሚከበረው የህብር ቀን በጋራ ለማክብር የቀረበ ጥረ

ኢትዮጵያና ኦማን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር ተወያዩ(ሪያድ፣ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) — በሳዑዲ አረቢያና በኦማን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አም...
06/09/2026

ኢትዮጵያና ኦማን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብራቸውን ለማጠናከር ተወያዩ

(ሪያድ፣ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) — በሳዑዲ አረቢያና በኦማን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር ከኦማን የንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ፈይሰል ቢን አብደላ አል ራዋስ ጋር በሁለትዮሽ የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ማጠናከር ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ ወቅት አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በኢነርጂ፣ በቱሪዝም እንዲሁም በባንክና ፋይናንስ ዘርፎች እያሳየችው ያለው ፈጣን ዕድገት ለኦማን ባለሀብቶች ሰፊ የኢንቨስትመንት ዕድል ይፈጥራል። አምባሳደሩ አክለውም የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ የሁለቱን ሀገራት ዘላቂ ዕድገትና የጋራ ተፎቃቃሪነት ለማረጋገጥ መሠረታዊ መሣሪያ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተውበታል።

የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሼኽ ፈይሰል ቢን አብደላ አል ራዋስ በበኩላቸው የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴና የልማት ምጥቀት አድንቀዋል። ኦማን ከበርካታ ሀገራት ጋር የነጻ ንግድ ስምምነት ያላት መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በቅድሚያ ትኩረት ከሚሰጣቸው ሀገራት አንዷ መሆኗን ገልጸዋል። ሁለቱ ሀገራት ጥራት ባላቸው ምርቶች ላይ በጋራ በመሥራት ምርቶችን ለዓለም ገበያ ማቅረብ የሚችሉበት ሰፊ ዕድል እንዳለም አመልክተዋል። አክለውም የኦማን የንግድ ልዑካን ቡድን በቅርቡ በኢትዮጵያ በየዘርፉ የተከፋፈሉ የሥራ ጉብኝቶችን እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

ሁለቱ ወገኖች በግብርና፣ በማዳበሪያ ምርት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በቱሪዝም እና በፋይናንስ ዘርፎች ያለውን ትብብር የበለጠ ለማስፋፋት የተስማሙ ሲሆን፤ የባህርና የአየር መጓጓዣ ትስስርን ማጠናከር፣ የወደብ አማራጮችን ማብዛት እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሙስካት ተጨማሪ መዳረሻዎችን ለማስጀመር ያደረገውን ዝግጅት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።

በተጨማሪም የጋራ የንግድ ምክር ቤት በመመሥረት በሁለቱ ሀገራት የግል ዘርፍ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል።

በዚሁ የሁለትዮሽ ውይይት ላይ በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሚሲዮኑ ምክትል መሪ ክቡር አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ እና ሌሎች ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል።

የክቡር አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር የኢትዮጵያ ኦማን ግንኙነት እና ሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር ጉብኝት======================================================...
06/09/2026

የክቡር አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር የኢትዮጵያ ኦማን ግንኙነት እና ሁለትዮሽ ትብብር ማጠናከር ጉብኝት
============================================================
(ሪያድ፣ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም.) በሳዑዲ አረቢያና በኦማን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶ/ር ሙክታር ከድር በኦማን ሱልጣኔት ለሽኝት ሥነ-ሥርዓት በመገኘት ከክቡር ሼኽ ኻሊፋ ቢን አሊ አል-ሐሪሲ፣ በኦማን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፖለቲካ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ጋር ተወያይተዋል። በዚህ ውይይት ላይ የኢትዮጵያና የኦማን መንግሥታትና አመራሮች መካከል ያለው የወዳጅነት ትስስር እጅግ መጠናከሩን አመልክተዋል።

ሁለቱ አመራሮች የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በታሪካዊ አጋርነት የተመሠረተ መሆኑን አስታውሰው፣ ኢትዮጵያ ለኦማን ያላትን ቅርበት እና ምቹ አካባቢ በመጠቀም በሁለቱ ሀገራት ያለውን ጠንካራ ትብብር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በግብርና፣ በማዳበሪያ ምርት፣ በቱሪዝም እና በሌሎች ዘርፎች የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ መንገዶችን ተወያይተዋል። እንዲሁም በቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ምክክር አድርገዋል።

ክቡር ሼኽ ኻሊፋ ቢን አሊ አል-ሐሪሲ በበኩላቸው፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ፣ ሕጋዊ የሥራ ስምሪትን ለማሳለጥ፣ የባህርና የአየር ትራንስፖርት ትስስርን ለማስፋፋት እንዲሁም በባንክና ፋይናንስ፣ በግብርና፣ በማዳበሪያ ምርት፣ በቱሪዝም እና በጤና ዘርፎች ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ሰፊ እድል መኖሩን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም ደረጃ እያስፋፋ ያለውን አገልግሎት፣ በቅርቡ በሀገራችን በመገኘት የጎበኙትን የቱሪዝም መዳረሻዎች እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች አድንቀው፣ የኦማን ኩባንያዎች በተለይም በኢነርጂ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በግብርና ዘርፎች በኢትዮጵያ እንዲሰማሩ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።

ዶ/ር መሐመድ አሊ አል-ባሉሺ፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ክፍል ኃላፊ፣ ከሪያድ ኤምባሲ ጋር በቅንጅትና በጥሩ ትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፣ ታሪካዊ ትስስር ያላቸው ሁለቱም ሀገራት በበርካታ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ማጠናከር እንደሚችሉ እና የጋራ ስምምነቶችን ማዕቀፍ ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል። የጋራ የንግድ ምክር ቤት በመመሥረት የሁለቱን ሀገራት የንግድ ትስስር በበለጠ ለማጠናከር ጠቃሚ መንገድ መሆኑን፣ ከሪያድ ኤምባሲ ጋር የመከሩት አንዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዋና ከተማ ሙስካት ተጨማሪ መዳረሻ ለማስጀመር ዝግጅቱ መጠናቀቁን አንዱ ግልጽ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

ክቡር መሐመድ ቢን ናስር አል-መብሳሊ በኦማን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዮች ክፍል ኃላፊ፣ በኦማን የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዜጎችን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ ከሪያድ ኤምባሲ ጋር በቅርበትና በተቀናጀ መልኩ ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም የኢትዮጵያዊያን ዜጎች ጉዳይ ከዚህ በተሻለ በተደራጀ መልኩ አስፈላጊውን ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ክቡር አምባሳደር በሽኝቱ ወቅትም በአጭር ጊዜ ውስጥ በኦማን ህዝብ የተሰጣቸውን ቅን አቀባበልና ደግነት በልዩ ሁኔታ አመስግነው፣ ሰላምታቸውን ለክቡር የኦማን ንጉስ አቅርበዋል።

በውይይቱም ላይ በሪያድ የኢፌዴሪ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን መሪ ክቡር አምባሳደር አወል ወግሪስ ሙሃመድ እና ዲፕሎማቶች ተሳትፈዋል።

ማስታወቂያወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ በማውጣት/በመስጠት ለአሻራ ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ እሁድ በቀን (06/09/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆ...
05/09/2026

ማስታወቂያ
ወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ በማውጣት/በመስጠት ለአሻራ ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ እሁድ በቀን (06/09/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 1:00 (7:00 AM) ሰዓት መለዝ አከባቢ በሚገኘው የአሻራ መስጫ ማዕከል ቀደም ብላችሁ በቦታው በመገኘት በስማ/አሻራ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ቦታው📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA?g_st=ic

BEEKSISA
Lammiiwwan gara biyyaa galuuf koppii liiseepaasee baafattanii/Kennitanii eeggachaa jirtan, Guyyaa borii Dilbata/Alhada (06/09/2026) ganama sa'aatii 1:00 AM (7:00 AM) irratti wiirtuu ashaaraa qubaa naannoo Malaz jedhamutti waqtiin dhufuun ashaaraa qubaa kennuu akka dandeessan isin beeksifna.
Iddoon:📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA

تطوير مشاريع الطاقة الكهرومائية واسعة النطاق، ومشاريع المنتجين المستقلين للطاقة (IPPs)، وربطها بالشبكة الكهربائية، وتجار...
03/09/2026

تطوير مشاريع الطاقة الكهرومائية واسعة النطاق، ومشاريع المنتجين المستقلين للطاقة (IPPs)، وربطها بالشبكة الكهربائية، وتجارة الطاقة النظيفة العابرة للحدود في منطقة شرق أفريقيا.

01/09/2026
31/08/2026
29/08/2026

አዲሱን የኢ-ፓስፖርት አገልግሎት በተመለከተ የተዘጋጀ የማመልከቻ መንገዱን የሚገልፅ አጭር ቪዲዮ
======================

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ.የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሀገር ውስጥ ብቻ ይሰጥ የነበረውን አዲሱን ኢ-ፓስፖርት ከSeptember 2026 ጀምሮ በሪያድ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ኤምባሲ መስጠት ጀመረ።

ይሄን የኢትዮጵያን ታሪክ በውል በመተረክ የሀገርን ገፅታና መልካም ስም ከፍ ያደረገውን አዲሱን ኢ-ፓስፖርት ለማግኘት ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ ላይ በመመዝገብ ክፍያውን ኦንላይን በመክፈል ቀጠሮ መያዝ ይችላሉ።
🔗 https://immigration.gov.et

የማመልከቻ ሂደቱም:-
1. Create Account ፣ አካውንት መክፈት፣
2. Apply (fill the forms, upload required docs, select your nearest embassy,select appointment slot) ፣ አስፈላጊ መረጃ መሙላት ፣ በቅርብ ያለን ኢምባሲ መምረጥ፣
3. complete your payment online፣ ክፍያውን በድረ-ገፁ ላይ ኦንላይን መፈፀም፣
4. Submit ፣ ማመልከቻው ማስገባት እና በቀጠሮው ቀን በቆንስላ ጽ/ቤታችን በአካል በመቅረብ ሂደቱን መጨረስ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ℹ️ ለበለጠ መረጃ:- የተዘጋጀውን ቪዲዮ በጥሞና ይመልከቱ።

ማስታወቂያወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ ኮፒ በመስጠት ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ እሁድ በቀን (30/08/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ...
29/08/2026

ማስታወቂያ
ወደ ሀገር ለመሳፈር ሊሴፓሴ ኮፒ በመስጠት ወረፋ ስትጠባበቁ የነበራችሁ ስማችሁ ቀጥሎ የተዘረዘረ ዜጎች ነገ እለተ እሁድ በቀን (30/08/2026) በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ 1:00 (7:00 AM) ሰዓት መለዝ አከባቢ በሚገኘው የአሻራ መስጫ ማዕከል ቀደም ብላችሁ በቦታው በመገኘት በስማ/አሻራ መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
ቦታው📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA?g_st=ic

BEEKSISA
Lammiiwwan gara biyyaa galuuf koppii liiseepaasee keessan kennattanii eeggachaa jirtan, Guyyaa borii Dilbata/Alhada (30/08/2026) ganama sa'aatii 1:00 AM (7:00 AM) irratti wiirtuu ashaaraa qubaa naannoo Malaz jedhamutti waqtiin dhufuun ashaaraa qubaa kennuu akka dandeessan isin beeksifna.
Iddoon:📌https://maps.app.goo.gl/a81KhiFUmEJhfQnCA

Address

Abu Bakr Al Karkhi, Al Safarat
Riyadh
11693

Opening Hours

Monday 8:30am - 3pm
Tuesday 8:30am - 3pm
Wednesday 8:30am - 3pm
Thursday 8:30am - 3pm
Sunday 8:30am - 3pm

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Embassy in Riyadh / የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ሪያድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share