ኢዜማ የአለምአቀፍ ድጋፍ ማህበር-Ezema International Support Association

ኢዜማ የአለምአቀፍ ድጋፍ ማህበር-Ezema International Support Association Citizens for Social Justice International

03/12/2025
03/11/2025
03/10/2025

“የተቋማት ግንባታው ይበልጥ ወደፊት መራመድ ሲገባው ወደ ኋላ የተመለሰበትን አግባብ እያስተዋልን ነው”

ቃልኪዳን ከበደ የኢዜማ በጀትና ፋይናንስ/ትሬዥረር መመሪያ ኃላፊ

በኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የምትዘጋጀው የዜጎች ልሳን መጽሔት ቅጽ 02_ቁ: 11 ትኩረቷን በተቋማት ግንባታ ላይ አድርጋ የተሠናዳች ሲሆን የወሩን እንግዳ ጨምሮ የተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮችን ታሥነብበናለች፤ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ሙሉውን ይዘት ያንብቡ።

https://drive.google.com/file/d/1mo5NeeWewZ79jZc_twPEX0OuajVGqTVq/view?usp=drivesdk

#ኢዜማ

03/08/2025

ለፖለቲካ ፍጆታ በሚል የሚደረጉ የሴቶች ተሳትፎን ኢዜማ እንደማይቀበል ያሣውቃል!!

የሰው ልጆች ሰው በመሆናቸው ብቻ ከሚጎናጸፉት ሰብዓዊ መብት ባሻገር የአንድ ሀገር ዜጋ ከመሆን የሚመነጩ ዴሞክራሲያዊ መብቶችም አሉ።

እንደ አጠቃላይ የሰው ልጆች እንደ ሁኔታው በተለያዩ ጊዜያት እነዚህን መብቶች በቅጡ ባለመከበራቸው እነዚህን መብቶች ለማስከበር ከፍተኛ ትግል እና መስዋዕትነት ተከፍሏል።

እነኚህ ከፍተኛ ትግሎች ቢደረጉም የሴቶች መብት መከበር ከተወሰኑ መሻሻሎች ባሻገር አሁንም ገና ብዙ የሚቀረው ሆኖ እናገኘዋለን።

ሴቶች የዓለምን ግማሽ በመቶ የሚሆን ቁጥር ቢይዙም ይህንን የሚመጥን በቂ እና ውጤት የሚያመጣ ውክልና ግን ኖሯቸው አያውቅም፤ ይልቁንም በዓለም ላይ ባሉ ሰው ሰራሽም ሆነ ተፈጥሯዊ አደጋ ከፍ ያለውን ዋጋ ከሕፃናት ጋር ሲወስዱ እንመለከታለን። ከዚህ በተጨማሪም እንደ መደፈር፣ ጠለፋ እና የመሣሠሉ የተለያዩ አይነት ጥቃት ሰለባዎችም ናቸው።

ለዚህ በዋነኛነት የማኅበረሰብ አረዳድ እና የመንግሥት አስፈላጊው የሕግ ሽፋን አለመሥጠት በመሠረታዊነት የሚነሱ ሲሆኑ ከእነዚህ ሁለቱ የመነጩ ታሪካዊ ኢፍትሐዊነቶች ሴቶች መብቶቻቸውን በተሟላ ሁኔታ ለመጠየቅ የሚያስችላቸው አቅምን እንዳያጎለብቱ ከፍ ሲል ለእነርሱም ምቹ የሆነ ሥርዓት መገንባት አለመቻል ምክንያት ሆኗል።

የዘንድሮ ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ጭብጥ (Theme) "ሁሉም መብቶች፤ ለሁሉም ሴቶች" በሚል ይከበራል።

ይህም ጭብጡ ካለፉት ጊዜያት ውስን ጉዳይ ላይ ካተኮረ ጭብጥነት ይልቅ ሰፋ ያሉ ጉዳዮችን የሚመለከት ሆኖ ተቀርጿል።

ይህ መሠረታዊ የሆኑ የመብት እና እኩልነት ጥያቄዎችን አንግቦ የተነሣው ጭብጥ በይደር የሚቆይ ሳይሆን ባለው አቅም ሁሉ ዛሬ ላይ እየተተገበረ መሔድ ያለበት ሆኖ እናገኘዋለን።

ይህንን ተግባር በእውነት ተፈፃሚ ለማድረግ ግን በመጀመርያ ስለችግሩ አንገብጋቢነት ጆሮ ሰጥቶ ከመስማት አንስቶ እስከ በበቂ ሁኔታ ችግሩን ለማስወገድ ፍላጎት ማሣደር እና አቅምን መገንባት ይሻል፤ ለዚህም በዚህ ውስጥ የሚመለከታቸው የሲቪክ ማኅበራት እንደ አጠቃላይ በሴቶች መብት ላይ በቂ ግንዛቤ መፍጠር፣ አስፈላጊ የሕግ ማዕቀፎችን በማነሳሳት እንዲወጡ ግፊት ማድረግ እና የመሣሠሉት ይጠበቃል፤ መንግሥት ችግሩን የሚመጥን የፖሊሲ እና ሕግ ማዕቀፍ አበጅቶ ሴቶች ለሀገራቸው እንደማንኛውም ዜጋ ሊያበረክቱ የሚገባቸው ላይ እንዲያተኩሩ ማድረግ እና ማኅበረሰቡ ሴቶች በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ የሚገጥሟቸውን ፈተናዎች አብሮ በመቆም ፍትሐዊ እና የተረጋጋ ማኅበረሰብ መፍጠር ላይ ሁሉም የድርሻቸውን እንዲወጡ ይጠበቃል።

ኢዜማ በማኅበራዊ ፕሮግራሙ በግልጽ እንዳስቀመጠው ሴቶችን ያገለለ ማንኛውም ዓይነት ፖሊሲ ውጤታማ እንደማይሆን ይገነዘባል፡፡ በተለይ የሴቶች በፖለቲካው መስክ መሳተፍ የራሳቸውን ጉዳይ በጥልቅ ያገናዘበ ፖሊሲ ለመቅረፅ ፋይዳው የጎላ እንደሚሆን ያምናል፡፡ ትምህርት ለእኩል ተሣትፎ ወሣኝ መሣሪያ በመሆኑ ሴት ልጆች ከትምህርት ገበታ የሚያስቀሩ ማነቆዎችን በማስወገድ ዘላቂ የሆነ የሴቶች ተሳትፎን ለማረጋገጥ ይሠራል፡፡ ሴቶች አሁን ያለው የፖለቲካ ምህዳር የፈጠረው አፈና ሲነሣ ሙሉ ኃይላቸውን ሊጠቀሙ የሚችሉበት እድል እንደሚፈጠር ኢዜማ ያምናል፡፡ ለይስሙላ ለፖለቲካ ፍጆታ በሚል የሚደረጉ የሴቶች ተሳትፎን #ኢዜማ እንደማይቀበልም ያሣውቃል።

እንኳን ለዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን አደረሣችሁ!!

03/08/2025
03/06/2025

ከተለያየ ዓይነት ማንነቱ በበለጠ አንድ ኢትዮጵያዊነቱ ያስተባበረው፤ የአንዲት ሀገሩንም የግዛት አንድነት ያስከበረ በወርሃ የካቲት የተፈጸመ ሌላ የጋራ መስዋዕትነት እና አኩሪ ታሪክ!! አንድ ሕዝብ እንጂ ሕዝቦች እንዳልሆንን ማሣያ ግማድ፤ ካራማራ!!

እንኳን ለ 47ኛው የካራማራ የድል በዓል መታሠቢያ ቀን አደረሣችሁ።

#ኢዜማ
#ኢትዮጵያ

03/02/2025

የእናት የአባቶቻችንን ድል የብሔር ሸማ ለማልበስ መድከም መሥዋዕትነታቸውን ማሳነስ መሆኑን ልብ ልንል ይገባል!

ኢትዮጵያ ሀገራችን በሕዝቧ መሥዋዕትነት ኢትዮጵያዊ ማንነቱን አስጠብቀው፣ ነፃነቱን አጽንተው ወደ ትውልድ ያስተላለፉ እናትና አባቶች ልጆች መሆናችንን እያሰብን የዛሬን ድል ማክበር ትልቅ ኩራት ነው።

የዚህ ድል ምንነት ሲገለጥ ድሉ ከሀገራችንም ተሻግሮ ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ እንደሆነ በተደጋጋሚ የሰማነው ነው፡፡ ይህ እውነት ሆኖ ዝንት ዓለም የሚኖር መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህን ድል ስናከብር ልናስታውሰው የሚገባው በዚህ ድል ቀደምት እናት አባቶቻችን ያስተላለፉልንን አንድነት፣ እኩልነት ነፃነት እና ሉዓላዊነት የሚባሉ አዕማዳትን ነው።

እነኚህ በከፍተኛ ተጋድሎ የተሻገሩልን መሠረታዊ ሐሣቦች አሁን ላይ ምን ያህል እንደ ዕሴት አቆይተናቸዋል የሚለውን ቆም ብሎ አስቦ ምላሽ መስጠት ያስፈልጋል።

ከዚህ አዕማድ አንፃር ሀገራችን የተከፈለው መሥዋዕትነት ለበለጠ አንድነት መሠረት የሚሆን ሆኖ ሳለ አሁን ላይ የዘውጌ ማንነት ላይ በተንጠለጠለ ፖለቲካ ሳቢያ መሠረቱ እየተነቀነቀ መሆኑን ስናስተውል በመሥዋዕትነት የተገኘ ድል ብለን ከምንገልጽባቸው ምክንያቶች አንዱን ጥያቄ ውስጥ እንዳለ ማሰብም ብሎም መፍትሔ መፈለግም ይኖርብናል፡፡

ሌላው መሠረታዊ ሐሣብ እኩልነት ሲሆን የሰው ልጅ የተለያየ ማንነት መገለጫ የሆኑት እንደ ቀለም ያሉት የእኩልነት መመዘኛ መስፈርቶች ልክ እንዳልሆኑ በማሣየት ረገድ ይህ ድል ትልቅ ነፀብራቅ ቢሆንም ሀገራችን ባለፉት ዓመታት ይህንን ማጽናት በማይችል የዘውጌ ማንነት ላይ በተንጠለጠለ ፖለቲካ ውስጥ በመውደቋ ለተለያዩ ዕድሎች እኩል መጫወቻ ሜዳ ከሚሠጥ ሥርዓት ውጪ ሆና ስናገኛት መልስ ልንፈልግለት እንደሚገባ ማሠብ አለብን።

በተጨማሪም ማሰብ ያለብን ስለ ነፃነት ሲሆን በተለይ ሀገራችን ዜጎቿ በማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳይ ተደራጅተው ለመንቀሳቀስ አስቻይ ያልሆኑ አምባገነናዊ ሥርዓት በተደጋጋሚ መዘወር እንዲሁም ከዚህ አምባገነናዊ ሥርዓት ላይ የዘውጌ ማንነት ላይ የተንጠጠለ ፖለቲካ ተደምሮበት ስንት መሥዋዕትነት በተከፈለባት ሀገር ላይ በነፃነት መዘዋወር አለመቻላችን ስናይ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ የሚለውን እንድናስብ ያስገድደናል።

ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች እና ሌሎች ጉዳዮች ተዳምረው ዝቅተኛ የምጣኔ ሀብት ደረጃ ላይ የምትገኝ ሀገር መሆኗ እና ዜጎቿ በድህነት አረንቋ ውስጥ መገኘት ሉዓላዊነቷን የምታመቻምችበት (compromise) ኢትዮጵያ መሆኗንም ሳይዘነጉ ምላሽ ይፈልጋል።

ለዚህ ደግሞ ሁላችንም ተጠያቂ መሆናችንን በመረዳት ከውይይት የተነሣ መፍትሔ ላይ ያተኮረ ተግባርን በመከተል የራሣችንን ዓድዋ እናሣካ ስንል ጥሪ እያስተላለፍን፤ በዓሉ ሲከበር የእናት የአባቶቻችንን ድል የብሔር ሸማ ለማልበስ መድከም መሥዋዕትነታቸውን ማሳነስ መሆኑን ልብ ልንል ይገባል!

ድሉም ልዩነታችንን በማጉላት ሳይሆን አንድነታችንን በሚመጥን መልኩ መከበር አለበት እንላለን፡፡ በተጨማሪም በዓሉ በሀገር መከላከያ ኃላፊነት መከበሩ መልካም ሆኖ በዚያው ልክም ሕዝቡ በአደባባይ በነፃነት ተሳትፎ የሚያከብረው የድል በዓል ይሁን እንላለን፡፡

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኀበራዊ ፍትሕ ( #ኢዜማ)
የካቲት 23/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ፣ ኢትዮጵያ

02/21/2025

ፍትሐዊ ሽግግርን ማጠናከር ለተረጋጋ ቀጣይነት (Strengthening a Just Transition for a Sustainable Future)

ዛሬ በዓለምአቀፍ ደረጃ የሚከበረው የማኅበራዊ ፍትሕ ቀን "ፍትሐዊ ሽግግርን ማጠናከር ለተረጋጋ ቀጣይነት" (Strengthening a Just Transition for a Sustainable Future) በሚል ጭብጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ ይከበራል።

ዓለም ባለፉት ዓመታት በተለያየ መስክ ዕያሣየቻቸው ያሉ ለውጦች እና እያጋጠሟት ያሉ ችግሮች መነሻ በማድረግ ትኩረት እንዲሠጥበት ታላሚ ያደረገ ጭብጥ ነው።

ለውጦች ከሚባሉት መካከል፤ ዓለም ከከርሰ ምድር የነዳጅ ኃይል ተጠቃሚነት ወደ አረንጓዴ ኃይል ተጠቃሚነት እያደረገች ያለው ሽግግር እና ዓለም በቴክኖሎጂው ረገድ እንደ የሰው ሰራሽ ልኅቀት (AI) ላይ ዕያሳየችው ያለው እድገት ተጠቃሽ ሲሆኑ እንደ ችግር የሚነሱት ደግሞ ዓለም የገጠማት ያልተረጋጋ የምጣኔ ሀብት ሁኔታና ይህንን ተከትሎ የተፈጠረ የምጣኔ ሀብት ኢ-ፍትሐዊነት ያመጣው የማኅበረሰብ አለመረጋጋት፣ አመፃ እና የአየር ንብረት ለውጥ ሲሆን በተጨማሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ፍልሰት እና መፈናቀል በዚህ ውስጥ ይካተታሉ።

እነኚህ ለውጦች እና ችግሮች ይዘው ሊመጡ የሚችሉትን አሉታዊ ውጤቶችን ቀደሞ በማሰብ በማኅበራዊ ፍትሕ እሳቤ አርቆ መግዛት ካልተቻለ ዓለም ለከፍተኛ አደጋ እየተጋለጠች መሄዷ እንደሚቀጥል መረጃዎች ያሣያሉ።

ሀገራችንም ከዓለም የተነጠለች እንዳለመሆኗ እና በተጨባጭም ካለችበት የማኅበራዊ፣ ምጣኔ ሀብት (በተለይም የቴክኖሎጂ እድገት)፣ ፖለቲካዊ እና የሰላምና ደኽንነት እድገት እና ሁነት አንፃር ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች አሳሳቢነት ደረጃ የሚለያይ ሲሆን ነገር ግን ወደፊትን አስቦ የሚደረግ ተገቢ ዝግጅት እንደሚያስፈልግ አያጠራጥርም።

ለአብነትም ኢትዮጵያ እየገጠማት ያለው የምጣኔ ሀብት አለመረጋጋት ካለባት የብድር ጫና ጋር ተዳምሮ ለማኅበረሰብ የሚሠጡ አገልግሎቶች እና መሠረተ ልማቶች ላይ የበጀት ፈሰስ ለማድረግ መንግሥት ላይ እክል የሚፈጥር በመሆኑ የኑሮ ውድነትን በመጨመር እና የብር የመግዛት አቅም በመቀነስ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ከባድ አድርጎታል።

በእርግጥ መንግሥት ከአበዳሪ ተቋማት ጋር የብድር ማሸጋሸግ ሥምምነት ሙከራ ቢያደርግም የወሰዳቸው የወጪ ቅነሣ እርምጃዎች ለማኅበረሰቡ ሊውሉ የሚችሉ አገልግሎት እና ሊሟሉ የሚገባቸው መሠረተ ልማቶችን በመገደብ እንዲሁም ተደራራቢ ግብር በመጣል ገቢ ለመሰብሰብ ላይ ትኩረት ማድረጉ ለዘላቂ ልማት እንቅፋት ከመሆኑ ባሻገር ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ዜጎች ላይ ሕይወትን የበለጠ ከባድ ያደርጋል።

#ኢዜማ ይህንን ችግር ለመፍታት የምጣኔ ሀብት ማሻሻያዎች ለማኀበራዊ ፍትሕ ቅድሚያ መስጠት እንዳለባቸው ያምናል በዚህም መሠረት ከላይ ለተጠቀሰው ችግር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች የእዳ ቀውሶችን እንዳይሸከሙ ማድረግ ያሻል ብሎ ያምናል፤ ሌሎች ተመሣሣይ ለውጦችና ችግሮችም እንደየሁኔታቸው በተመሣሣይ የምላሽ ማዕቀፍ ውስጥ ፍትሐዊ ሽግግርን የተረጋጋ ቀጣይነት ባረጋገጠ መልኩ መፍትሔ ሊሠጣቸው ይገባል ብሎ ያምናል።

02/19/2025

የኢትዮያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የየካቲት 12 ሰማዕታት በተገቢው መልኩ መዘከር አለባቸው ብሎ ያምናል።

#ኢዜማ በዘመናት ለሀገራችን የተከፈለውን ውድ ዋጋ ያከብራል፤ ይዘክርማል!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ
የካቲት 12/2017

02/14/2025

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ( #ኢዜማ) ሀገራዊ ምክክሩን በተመለከተ እየሰበሰበ ይገኛል፤ በመሆኑም ከታች ያለውን ማስፈንጠርያ በመጫን አስተያየትዎን ይስጡን።

መጠይቁን ከዛሬ የካቲት 07/2017 ዓ.ም. እስከ የካቲት 17/2017 ዓ.ም. ባለው ጊዜ መሙላት እይደሚቻል እያሣወቅን ስለሚደረግልን ትብብር ሁሉ ከወዲሁ እናመሠግናለን።

https://ee.kobotoolbox.org/x/WlMMRUv5

02/11/2025

በ #ኢዜማ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የምትዘጋጀው የዜጎች ልሳን መጽሔት ቅጽ 02_ቁ: 010 የወሩን እንግዳ ጨምሮ በዚህ ዕትም

👉 የኑሮ ውድነቱን እያባባሰ ያለው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ

👉 ብልጽግና ፓርቲ እና ሰሞነኛው ጠቅላላ ጉባኤው

👉 አወዛጋቢው የንብረት ማስመለስ አዋጅ ያስከተለው ስጋት የሚሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን ታስነብበናለች

ማስፈንጠሪያውን በመጫን ሙሉውን ይዘት ያንብቡ።

https://drive.google.com/file/d/1HArivJ-5f8No7lqUzyKO5jPSM3ZKyEKN/view?usp=drivesdk

#ኢዜማ

Address

8647 Richmond Highway
Alexandria, VA
22309

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢዜማ የአለምአቀፍ ድጋፍ ማህበር-Ezema International Support Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ኢዜማ የአለምአቀፍ ድጋፍ ማህበር-Ezema International Support Association:

Videos

Share